መዝሙር 100 (NASV)
መዝሙር 100
የምስጋና መዝሙር።
1ምድር ሁሉ ለእግዚአብሔር እልል በሉ፤
2 እግዚአብሔርን በደስታ አገልግሉት፤
በፍሥሓ ዝማሬ ፊቱ ቅረቡ።
3 እግዚአብሔር አምላክ መሆኑን ዕወቁ፤
እርሱ ፈጠረን፤ እኛም የርሱ ነን100፥3 ወይም እና ራሳችንን አይደለንም፤
እኛ ሕዝቡ የማሰማሪያው በጎች ነን።
4በምስጋና ወደ ደጆቹ፣
በውዳሴም ወደ አደባባዮቹ ግቡ፤
አመስግኑት፤ ስሙንም ባርኩ፤
5 እግዚአብሔር ቸር፣ ምሕረቱም ለዘላለም ነውና፤
ታማኝነቱም ከትውልድ እስከ ትውልድ ነው።