መዝሙር 128 (NASV)

መዝሙር 128
መዝሙረ መዓርግ።
1ብፁዓን ናቸው፤
እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሁሉ፣
በመንገዱም የሚሄዱ፤
2የድካምህን ፍሬ ትበላለህ፤
ብፅዕና እና ብልጽግና የአንተ ይሆናሉ።
3ሚስትህ በቤትህ፣
እንደሚያፈራ ወይን ናት፤
ወንዶች ልጆችህ በማእድህ ዙሪያ፣
እንደ ወይራ ተክል ናቸው።
4እነሆ፤ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው፣
እንዲህ ይባረካል።
5 እግዚአብሔር ከጽዮን ይባርክህ፤
በሕይወትህ ዘመን ሁሉ፣
የኢየሩሳሌምን ብልጽግና ያሳይህ፤
6የልጅ ልጅ ለማየትም ያብቃህ።
በእስራኤል ላይ ሰላም ይውረድ።