መዝሙር 134 (NASV)

መዝሙር 134
መዝሙረ መዓርግ።
1እናንተ በሌሊት ቆማችሁ በእግዚአብሔር ቤት የምታገለግሉ፣
የእግዚአብሔር ባሪያዎች ሁላችሁ እግዚአብሔርን ባርኩ።
2በመቅደሱ ውስጥ እጆቻችሁን አንሡ፤
እግዚአብሔርንም ባርኩ።
3ሰማይንና ምድርን የሠራ እግዚአብሔር
ከጽዮን ይባርክህ።